የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮጵያ ትረስት ፈንድ 40 ሚሊየን ብር የሚገመት የህክምና ቁሳቁሶች ድጋፍ አደረገ

By Feven Bishaw

June 05, 2020

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 28 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ)የኢትዮጵያ ትረስት ፈንድ የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል የሚገመት 40 ሚሊየን ብር ግምት ያላቸው የህክምና ቁሳቁሶችን ለጤና ሚኒስቴር በድጋፍ አበረከተ።

ድጋፉ በዋናነት ቫይረሱን ለመከላከል ግንባር ቀደም ሆነው ለተሰለፉ የጤና ባለሙያዎች የሚውል መሆኑ ነው የተነገረው።