የሀገር ውስጥ ዜና

ምክር ቤቱ ነገ 17ኛ መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል

By ዮሐንስ ደርበው

March 13, 2024

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ 17ኛ መደበኛ ስብሰባውን እንደሚያካሂድ አስታውቋል፡፡

በስብሰባውም የአንድ የምክር ቤት አባል ያለመከሰስ መብት እንደሚነሳ ይጠበቃል መባሉን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

በተጨማሪም ዘጠኝ ረቂቅ አዋጆችን እንደሚያጸድቅ እና ሁለት ረቂቅ አዋጆችን ደግሞ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች እንደሚመራ ይጠበቃል።