አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ምርጥ ዘር ድርጅት የመጀመሪያውን የምርጥ ዘር ምርት መሰብሰብ መጀመሩን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር ገለጹ፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ ድርጅቱ የምርጥ ዘር ምርት መሰብሰብ መጀመሩ ቀጣይ በክልሉ አቅም የምርጥ ዘር አቅርቦትን ለማሳለጥ ዓይነተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡