የሀገር ውስጥ ዜና

የባህር ሃይል ጠቅላይ መምሪያ አባላት የአድዋ ድል መታሠቢያን ጎበኙ

By Mikias Ayele

March 23, 2024

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የባህር ሃይል ጠቅላይ መምሪያ አባላት የአድዋ ድል መታሠቢያን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የባህር ሃይል አባላት የአድዋ ድል ዘመን ተሻጋሪ መሆኑን ገልፀው÷ ታሪካዊ የሆነውን መታሠቢያ በመጎብኘታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።

እንዲሁም የአድዋ ድል መታሠቢያ ብዙ ታሪካዊ እውነታዎችን የያዘ መሆኑን የገለፁ ሲሆን÷ በመጎብኘታቸው  ልዩ ስሜት እንደፈጠረባቸው መናገራቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ፌስቡክ ገፅ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡