የሀገር ውስጥ ዜና

በወምበራ ወረዳ ከ155 ሚሊየን ብር በላይ የተገነቡ ሁለት የመንገድ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ

By Tibebu Kebede

June 08, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በወምበራ ወረዳ ከ155 ሚሊየን ብር በላይ የተገነቡ ሁለት የመንገድ ፕሮጀክቶችን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን መርቀው ከፍተዋል።

የመንገድ ፕሮጀክቶቹ በወምበራ ወረዳ ከደብረዘይት – ሳንቂ – መልካን እና ከገሰንገሳ – ወግዲ የሚያገናኙ ናቸው።