የሀገር ውስጥ ዜና

የኦሮሚያ ልማት ማህበር የአዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ

By Mikias Ayele

March 25, 2024

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ልማት ማህበር (ኦልማ) ልዩ የአዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል::

በጉብኙቱ ወቅት ተማሪዎቹ የዓድዋ ድል መታሰቢያን በመጎብኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡

በመንግስት የተሰራው ስራ እነሱም ወደፊት ለሀገራቸው በጎ እና ለትውልድ የሚተላለፍ ታሪክ ሰርተው እንዲያልፉ እንዳነሳሳቸው መናገራቸውን ከከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡