አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 3 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር የውሃ ልማት ኮሚሽንና የልማት አጋሮች ኮሮናን ለመከላከል እና የውሃ አቅርቦትን ለማሻሻል የሚረዱ በ13 ሚሊየን ብር የተገዙ 34 ፓምፖችን ለክልሎች ተከፋፈሉ።
በውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር ነጋሽ ዋጌሾ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ፥ የውሃ ልማት ኮሚሽንና የልማት አጋሮች የኮሮና ስርጭትን ለመግታት የውሃ አቅርቦትን ለማሻሻል በጥምረት እየሠሩ መሆኑን ተናግረዋል።