አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ ከበጎ ፈቃደኞች ጋር በመሆን በምግባችን ከጓሯችን መርሃ ግብር ችግኝ ተክለዋል።
ከተማ አስተዳደሩ ያስጀመረውን የክረምት በጎ ፍቃድ አስመልክቶ ነው ምክትል ከንቲባው ከ50 የአዲስ አበባ ሰፈሮች የተውጣጡ 50 በጎ ፍቃደኞች ጋር በመሆን በመዘጋጃ ቅጥር ግቢ ውስጥ ችግኝ ተከላ ያካሄዱት።