የሀገር ውስጥ ዜና

ኢንጅነር ታከለ ኡማ ከበጎ ፈቃደኞች ጋር በመሆን በምግባችን ከጓሯችን መርሃ ግብር ችግኝ ተከሉ

By Meseret Awoke

June 11, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ ከበጎ ፈቃደኞች ጋር በመሆን በምግባችን ከጓሯችን መርሃ ግብር ችግኝ ተክለዋል።

ከተማ አስተዳደሩ ያስጀመረውን የክረምት በጎ ፍቃድ አስመልክቶ ነው ምክትል ከንቲባው ከ50 የአዲስ አበባ ሰፈሮች የተውጣጡ 50 በጎ ፍቃደኞች ጋር በመሆን በመዘጋጃ ቅጥር ግቢ ውስጥ ችግኝ ተከላ ያካሄዱት።