የሀገር ውስጥ ዜና

ምዕመኑ የትንሳኤ በዓልን ሲያከብር ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን በማገዝ እንዲሆን ተጠየቀ

By ዮሐንስ ደርበው

May 04, 2024

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምዕመኑ የትንሳኤ በዓልን ሲያከብር ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን በማገዝ ሊሆን እንደሚገባ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስትያናት ካውንስል ዋና ጸሐፊ ቄስ ደረጄ ጀምበሩ አስገነዘቡ፡፡

ዋና ጸሐፊው ለትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸውም÷ ምዕመኑ የትንሳኤ በዓልን ሲያከብር ዕርዳታና ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ወገኖች በማገዝ ሊሆን ይገባል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

በክርስቶስ ትንሳኤ ሁሉም በፍቅር ልብና በይቅርታ ለሰላምና አብሮነት በመጸለይ በዓሉን እንዲያከበርም ጠይቀዋል፡፡