አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦማን ማቆያ ጣቢያዎች ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን መካከል 230 ያህሉ ዛሬ ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
እንዲሁም በኦማን የሚገኙ 1 ሺህ 590 ኢትዮጵያውያንን ዛሬና ሐሙስ በሚደረጉ ሥድስት በረራዎች ወደ ሀገራቸው ለመመለስ መታቀዱን ነው ሚኒስቴሩ ያስታወቀው፡፡
ዛሬ ለተመለሱት ወገኖችም አስፈላጊውን እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ሥራ እየተሰራ መሆኑ ተመላክቷል፡፡