የሀገር ውስጥ ዜና

የአማራ ክልል የቅሬታ ምንጭ ሆነዋል ባላቸው ሠራተኞች ላይ እርምጃ ወሰደ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 1፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) የአማራ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቅሬታ ምንጭ ሆነዋል ባላቸው ከ20 በላይ ሠራተኞች ላይ እርምጃ ወሰደ።

በ2011 ዓ.ም ከአስቸኳይ ጥገና፣ ከኃይል መቆራረጥና አዳዲስ ጥያቄዎች፣ ከቅድመ ቆጣሪ ክፍያ መስተንግዶ፣ ከንብረት አያያዝና አጠቃቀም እና ከሌሎች ጥያቄዎች ጋር በተያያዘ 13 ሺህ 441 ደንበኞች ቅሬታ ቀርበው ምላሽ እንደተሰጣቸው የክልሉ የኤሌክትሪክ አገልግሎት የሕዝብ ግኙነት ሥራ አስኪያጅ አቶ ማተቤ ዓለሙ ገልጸዋል።