የሀገር ውስጥ ዜና

የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ያስገነባቸውን ቤቶች አስተላለፈ

By Mikias Ayele

May 11, 2024

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን በኮየ ፈጬ እና በቃሊቲ ሳይቶች ያስገነባቸውን መኖሪያ ቤቶች ለተጠቃሚዎች አስተላለፈ።

በቤቶቹ ማስተላለፍ በስነ-ስርዓት ላይ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ቤቶቹ በመከላከያ ኢንጂነሪንግ እና ኦቪድ ኮንስትራክሽን አማካኝነት በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ተገንብተው የተጠናቀቁ መሆናቸው ተገልጿል።

በመራኦል ከድር