የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከደቡብ ኮሪያ አቻቸው ጋር ተወያዩ

By Feven Bishaw

June 12, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከደቡብ ኮሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካንግ ዩንግ ውሃ ጋር ዛሬ በስልክ ተወያዩ።

ሁለቱ ሚኒስትሮቸ የሁለቱን አገራት ግንኙነት ለማጠናከር፣ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን በትብብር ለመከላከል እና የኮሪያ ባለህብቶች በኢትዮጵያ ስለሚኖራቸው የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በተመለከተ ትኩረት አድርገው መክረዋል።