የሀገር ውስጥ ዜና

አምባሳደር ታዬ ከካናዳ ዓለም አቀፍ የልማት ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

By Mikias Ayele

May 13, 2024

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከካናዳ ዓለም አቀፍ የልማት ሚኒስትር አሕመድ ሁሴን ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም ÷አምባሳደር ታዬ ኢትዮጵያ ከካናዳ ጋር ላላት ጠንካራ ግንኙነት ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ አውስተዋል፡፡

ሁለቱ ወገኖች በሀገራቱ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ የጋራ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውንም የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

በተጨማሪም በኢትዮጵያ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ ማቋቋም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸው ተገልጿል፡፡