አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በከተሞች የሥራ ዕድል ፈጠራና የምግብ ዋስትና ፕሮግራም የታቀፉና በኮቪድ 19 ሳቢያ ለችግር ተጋላጭ የሆኑ የከተማ ልማት ሴፍቲኔት ተጠቃሚዎችን መደገፍ የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።
ስምምነቱ በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር፣ በሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በዩኒሴፍና በዓለም የምግብ ፕሮግራም መካካል ሲሆን፥ የተገኘው የገንዘብ ድጋፍ በኮቪድ19 ምክንያት የኑሮ ጫና የደረሰባቸውን ዜጎች ለመታደግ የሚያስችል ነው ተብሏል።