የሀገር ውስጥ ዜና

የሶማሊ ክልል የጎሳ መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የሀይማኖት መሪዎች የህዳሴ ግድብን እውን ለማድረግ ከመንግስት ጎን እንደሚቆሙ አረጋገጡ

By Tibebu Kebede

June 13, 2020

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 6 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሊ ክልል የሚገኙ የተለያዩ የጎሳ መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች የሀይማኖት መሪዎች በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከተወያዩ በኋላ የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡

የጎሳ መሪዎቹ፣ የሀገር ሽማግሌዎቹ እና የሀይማኖት መሪዎቹ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ እና የክልሉ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል።