አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በአዳማ ከተማ ተካሄዷል።
በመርሐ ግብሩ ላይ በም/ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አብዱልሃኪም ሙሉን ጨምሮ ሌሎች የክልሉና የአዳማ ከተማ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
አቶ አብዱልሀኪም በዚሁ ወቅት÷በአደማ ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚተዳደሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ቤት እድሳት አስጀምረዋል።
በተመሳሳይ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚከናወን የህፃናት መዋያ ማዕከል ግንባታም ተጀምሯል።
በክልሉ በተጀመረው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት12 ነጥብ 3 ሚሊየን ዜጎች እንደሚሳተፉ ተመላክቷል፡፡
በዚህም 46 ነጥብ 6 ቢለየን ብር የሚገመት ሥራ በማከናወን 4 ነጥብ 8 ሚሊየን ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱ ተገልጿል፡፡
በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ የአቅመ ደካሞች ቤት እድሳትና ግንባታ፣ የአካባቢ ጽዳት፣ ችግኝ ተከላ፣ የማጠናከሪያ ትምህርትን ጭምሮ በተለያዩ ዘርፎች እንደሚከናወን ተጠቁሟል፡፡
በሌሊሴ ተስፋዬና ኦሊያድ በዳኔ