አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሳዑዲ ባለሀብቶች በባለ 5 ኮከብ ሆቴል እና ሌሎች የቱሪዝም አገልግሎቶች ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው ገለፁ፡፡
የኢትዮ-ሳዑዲ የቢዝነስ እና ኢንቨስትመንት ፎረም ላይ ለተሳተፉ ባለሀብቶች በቱሪዝም ዘርፍ ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በተመለከተ ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡፡
ባለሀብቶቹ በተለይም በባለ 5 ኮከብ ሆቴል ኢንቨስትመንት ላይ መሳተፍ በሚችሉበት መንገድ ዙሪያ ከቱሪዝም ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጋር መምከራቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡