የሀገር ውስጥ ዜና

ሜጀር ጄኔራል ከፍያለው አምዴ ተሰማ በአብዬ ግዛት የተመድ የሰላም አስከባሪ ሃይል አዛዥ ሆነው ተሾሙ

By Tibebu Kebede

June 16, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ሜጀር ጄኔራል ከፍያለው አምዴ ተሰማን በአብዬ ግዛት የተሰማራው የተመድ የሰላም አስከባሪ ጦር ሀይል አዛዥ አድርገው ሾሙ።

ሜጀር ጄኔራል ከፍያለው አምዴ ተሰማ የስራ ጊዚያቸውን የፊታችን ሀምሌ ወር የሚያጠናቅቁትን ሜጀር ጄኔራል መሀሪ ዘውዴን ተክተው ይሰራሉ ተብሏል።