የሀገር ውስጥ ዜና

ደቡብ ኮሪያ በደን ሀብት መልሶ ማልማት እና ቀጣይነት ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ልትሰራ ነው

By Tibebu Kebede

June 17, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ደቡብ ኮሪያ እና ኢትዮጵያ የደን ሀብትን መልሶ ለማልማት እና ቀጣይነት ያለው የደን ልማትን በተለያዩ አካባቢዎች ለማረጋገጥ ሀገራቱ በትብብር ሊሰሩ ነው።

በደን ሀብት ልማት በጋራ መስራት የሚያስችለውን ስምምነትም የኢትዮጵያ አካባቢ፣ ደን እና የአየር ንብረት ኮሚሽን እና የደቡብ ኮሪያ የደን አገልግሎት ይፋ አድርገዋል።