የሀገር ውስጥ ዜና

በታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ የመጀመሪያው የውሃ ሙሌትን ለማከናወን መንግስት የያዘውን አቋም አጠናክሮ ሊቀጥልበት እንደሚገባ ምሁራን ገለፁ

By Tibebu Kebede

June 17, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ የመጀመሪያው የውሃ ሙሌትን ለማከናወን መንግስት የያዘውን አቋም አጠናክሮ ሊቀጥልበት እንደሚገባ ምሁራን ገለፁ።

ከፋና ብሮድካስቱንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት ምሁራኑ ፤ ግብጽ ባለፉት 5 ቀናት በተደረገው የ3ቱ ሀገራት ድርድር ያንጸባረቀችው ግትርነት የውሃ ሙሌቱን ከዚህ ክረምት ለማደናቀፍ ያሴረ ነው ብለዋል።