የሀገር ውስጥ ዜና

የኮቪድ 19 ወረርሽኝ የሩሲያ እና የኢትዮጵያን የንግድ ግንኙነቶችን አልገታም- አምባሳደር አለማየሁ ተገኑ

By Meseret Demissu

June 18, 2020

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሩስያ የኢትዮጵያ አምባሳደር አለማየሁ ተገኑ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ የኢትዮጵያን እና የሩሲያን የንግድ ግንኙነቶች አለማስቆሙን ገለጹ።

አምባሳደሩ ከሩስያ የዜና አገልግሎት ጋር በነበራቸው ቆይታ÷ ወረርሽኙ  በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትብብር አለማስቆሙን ጠቁመዋል ።

በዚህም ሁለቱም ወገኖች የጠበቀ ትብብራቸውን ጠብቀው እየተጓዙ በመሆኑ የሁለቱ አገራት ግንኙነት በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛልም ነው ያሉት ።

የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በቅርቡ የስልክ ውይይት ማድረጋቸውንአምባሳደሩ አስታውሰው÷ በዚህ በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ሩሲያ እና የኢትዮጵያ ያላቸው ኢኮኖሚያዊ ትብብርና የንግድ ግንኙነት በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል  ብለዋል፡፡

አምባሳደሩ በማሳያነትም “የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጭነት አውሮፕላኖች በሳምንት ሁለት ጊዜ“ ከሩሲያ ወደ አፍሪካ ፣ ከአፍሪካ ወደ ሩሲያ በማመላለስ በመስራት ላይ መሆኑን ” አንስተዋል፡፡

ከዚያም ባለፈ በባህላዊ  መስክ ያለው ትብብር   ጠንካራ ግንኑነት ላይ የተመሰረተ መሆኑን ጠቁመዋል።

በዚህም ታላቁ የሩሲያ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን በኢትዮጵያም ውስጥ እጅግ ተወዳጅ መሆኑን ጠቁመዋል።

አምባሳደሩ አክለውም ኤምባሲያቸው ከሁለቱም አገራት የተውጣጡ  6 ሺህ ሰዎች የሚሳተፉበት የቪድዮ የንግድ የውይይት መድረክ ማዘጋጀቱን ተናግረዋል።

አምባሳደሩ አያይዘውም በየዓመቱ ሰኔ 6 ቀን  የሩሲያ ቋንቋ ቀን በኢትዮጵያም እንደሚከበር ገልጸው÷ ቀኑን “ከሩሲያ ጓደኞቻችን ፣ ተማሪዎች ፣ ፕሮፌሰሮች ፣ የአፍሪካ ማህበረሰብ  ጋር በመሆን በጋራ እናከብራለን ብለዋል፡፡

በዚህ ዓመት በወረርሽኙ ምክንያት በአካል መገናኘት ከባድ  ቢሆንም  ቀኑን በቪድዮ ኮንፈንስ መከበሩን ጠቅሰዋል

ምንጭ፡-የሩስያ ዜና አገልግሎት