አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ግብፅ በህዳሴ ግድብ ላይ የምታነሳው ተቃውሞ ፖለቲካዊ እንጂ ሳይንሳዊ ምክንያት እንደሌለው ግብፃዊው የስነ ምድር ምሁር ፍሩዝ አልባዝ ተናገሩ።
ምሁሩ ከኤም ቢ ሲ ዓረብኛ ዩ ቲዩብ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት “የግድቡ ውሃ ሙሌት ግብፅን ለውሃ ዕጥረት ይዳርጋል” ተብሎ የሚወራው የግብጽ ፖለቲከኞችና መገናኛ ብዙሃኗ ፕሮፓጋንዳ እንጅ እውነታን የተከተለ አይደለም።