የሀገር ውስጥ ዜና

ግብፅ በህዳሴ ግድብ ላይ ያላት ተቃውሞ ፖለቲካዊ እንጅ ሳይንሳዊ ምክንያት የለውም – ግብፃዊ ምሁር

By Feven Bishaw

June 19, 2020

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ግብፅ በህዳሴ ግድብ ላይ የምታነሳው ተቃውሞ ፖለቲካዊ እንጂ ሳይንሳዊ ምክንያት እንደሌለው ግብፃዊው የስነ ምድር ምሁር ፍሩዝ አልባዝ ተናገሩ።

ምሁሩ ከኤም ቢ ሲ ዓረብኛ ዩ ቲዩብ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት “የግድቡ ውሃ ሙሌት ግብፅን ለውሃ ዕጥረት ይዳርጋል” ተብሎ የሚወራው የግብጽ ፖለቲከኞችና መገናኛ ብዙሃኗ ፕሮፓጋንዳ እንጅ እውነታን የተከተለ አይደለም።