ዓለምአቀፋዊ ዜና

ፕሬዚዳንት ትራምፕ በልጅነታቸው አሜሪካ ገብተው ያለ ህጋዊ ሰነድ ለሚኖሩ ስደተኞች ከለላ የሚሰጠው ፕሮግራም እንዲቋረጥ ያቀረቡት እቅድ ውድቅ ሆነ

By Feven Bishaw

June 19, 2020

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በልጅነታቸው አሜሪካ ገብተው ያለ ህጋዊ ሰነድ ለሚኖሩ ስደተኞች ከለላ የሚሰጠው ፕሮግራም እንዲቋረጥ ያቀረቡትን እቅድ ውድቅ አደረገ።

ፕሮግራሙ በፈረንጆቹ 2012 በይፋ የተጀመረ ሲሆን፥ ሌላ ሃገር ተወልደው በልጅነታቸው አሜሪካ የገቡና ለመኖር የሚያስፈልገውን ህጋዊ ሰነድ ለማያሟሉ ስደተኞች ከአሜሪካ እንዳይወጡ ከለላ የሚሰጥ ነው።