አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢ ምቹ፣ ተወዳዳሪና ተመራጭ ለማድረግ እንዲቻል በማቀድ በተቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ አማካኝነት ዋና ዋና የማሻሻያ ስራዎችን ማካሄድ መቻሉን ገልፀዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስ ቡክ ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ በተሰሩት የማሻሻያ ስራዎች ቁልፍ የሕግና የአስተዳደራዊ ለውጦችን ማስመዝገብ እንደተቻለ አስታውቀዋል።