የሀገር ውስጥ ዜና

ኢንተርኔትን መሰረት ያደረገ የትራንስፖርት ክፍያ አገልግሎት ተጀመረ

By Feven Bishaw

June 19, 2020

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢንተርኔትን መሰረት ያደረገ የትራንስፖርት ክፍያ አገልግሎት መጀመሩን የትራንስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

በዛሬው እለት በመናኸሪያዎች አካላዊ ርቀትን ለማስጠበቅ ከሚሰሩ ስራዎች መካከል ተጠቃሚዎች ትኬት ለመቁረጥ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ የሚፈጠር አካላዊ ጥግግት ለመቀነስ የሚረዳ ኢንተርኔትን መሰረት ያደረገ የትራንስፖርት ክፍያ አገልግሎት በይፋ ተጀምሯል፡፡