አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሂደት ለመዘግየቱ የፕሮጀክት አስተዳደር ችግሮች ዋነኛ እንቅፋት እንደነበረ የቀድሞው የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር አቶ ሞቱማ መቃሳ ተናገሩ፡፡
አቶ ሞቱማ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ ከለውጡ በፊት በፕሮጀክቱ ላይ የቦርዱ ሪፖርት ከግንባታ ሂደቱ ጋር ጭምር ያልተናበበ የውሸት አፈጻጸም ይገልጽ ነበር ብለዋል ።