አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በብራዚል የኮሮና ቫይረስ 50 ሺህ ለሚጠጉ ሰዎች ህይወት ማለፍ ምንያት መሆኑ ተነግሯል፡፡
ባለፉት 24 ሰዓታትም የሟቾች ቁጥር 1 ሺህ 22 ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
ሃገሪቱ የመጀመሪያውን በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው ያረጋገጠችው በየካቲት ወር መጨረሻ ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት ቁጥሩ አንድ ሚሊዮን መሻገሩ ተሰምቷል፡፡
እስካሁን ባለው መረጃ በአለም አቀፍ ደረጃ 8 ነጥብ 75 ሚሊየን ሰዎች በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሲሆን፥ ከ464 ሺህ በላይ ሰዎች ለህልፈት ተዳርገዋል፡፡
በተጨማሪም ከ4 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሰዎች በላይ ከኮሮና ቫይረስ ማገገማቸውን የጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ መረጃ ያመለክታል፡፡
ምንጭ፡- አልጀዚራ