አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በአርሲ ዞን የተለያዩ ልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ነው፡፡
በጉብኝት መርሐ ግብሩ ሌሎች የክልሉ የሥራ ሃላፊዎች መሳተፋቸውን የዞኑ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡
የሥራ ሃላፊዎቹ በትናንትናው ዕለት በክልሉ ምዕራብ አርሲ ዞን የተለያዩ የግብርና ልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።
በዛሬው ዕለትም በአርሲ ዞን የተለያዩ የግብርና ልማት ሥራዎችን በመጎብኘት ላይ እንደሚገኙ ተጠቁሟል፡፡