የሀገር ውስጥ ዜና

ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ

By ዮሐንስ ደርበው

August 17, 2024

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

ተመራቂዎቹ በምህንድስና፣ በጤና እና በሃብት አሥተዳደር ዘርፍ ትምህርታቸውን በመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ እንዲሁም በምህንድስና የትምህርት ዘርፍ በዶክትሬት ዲግሪ መከታተላቸው ተገልጿል፡፡

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስትርና የዩኒቨርሲቲው የቦርድ ሰብሳቢ ፍጹም አሰፋን (ዶ/ር) ጨምሮ የመከላከያ ሚኒስትር ዴዔታዎች፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖችና የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል።

በሦስት ኮሌጆች እና በአንድ የምርምር እና ልማት ኢንስቲትዩት የተዋቀረው ዩኒቨርሲወቲው÷ በመጪዎቹ ዓመታት በአፍሪካ ከሚገኙ ምርጥ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲዎች ቀዳሚ የመሆን ራዕይ አንግቦ እየሠራ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ከኢትዮጵያ ተማሪዎች በተጨማሪ ከጎረቤት ሀገራት የመጡ ተማሪዎችንም አሰልጥኖ እያስመረቀ መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል፡፡