የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ እንዳሻው ጣሰው እና ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) የወራቤ ንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክትን ጎበኙ

By Melaku Gedif

August 18, 2024

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው እና የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) የወራቤ ንጹህ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክትን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝቱ ወቅት የፕሮጀክቱ ተቋራጭ ÷ፕሮጀክቱ 80 ኪሎ ሜትር የመስመር ዝርጋታ እንደሚኖረው እና 60 ሺህ ሰዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ ኤሌክትሮ ሜካኒካል እቃዎች በመግባት ላይ መሆናቸውን ጠቁመው÷ የመብራት ተከላ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል፡፡

የፕሮጀክቱ የውሃ ጉድጓዶች እስከ 20 ዓመት አገልግሎት መስጠት እንደሚችሉ ነው የተመላከተው፡፡

የፕሮጀክቱን ግንባታ በ1 ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራም የፕሮጀክቱ ተቋራጭ ገልጸዋል፡፡

በኤርሚያስ ቦጋለ