የሀገር ውስጥ ዜና

ግብፅ አሁንም እንዲከበርላት የምትሻው የቅኝ ግዛት ዘመን የአባይ ውሃ ድርሻ ክፍፍል ምን ይመስላል

By Tibebu Kebede

June 23, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየገነባች ያለውን ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግብፅ በቅኝ ግዛት ዘመን የተፈረመውን የውሃ ድርሻዬን ይቀንስብኛል በሚል በመቃወም ላይ ትገኛለች።

ግብፅ አሁንም እንዲከበርላት የምትሻው የቅኝ ግዛት ዘመን የአባይ ውሃ ድርሻ ክፍፍል ስምምነት በብሪታኒያ አመቻችነት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1929 የተፈረመ ነው።