አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ሜታ ወረዳ ዱርሲቱ ቢሊሱማ ቀበሌ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የሥድስት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡
የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የኮሙኒኬሽንና ሚዲያ ክፍል ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ካሳዬ አበበ እንደገለፁት÷ አደጋው የተከሰተው ከአዲስ አበባ ወደ ጅቡቲ ይጓዝ የነበረ የነዳጅ ቦቴ ከባድ መኪና ከባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨታቸው ነው፡፡
የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑንም ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡
በተሾመ ኃይሉ