የሀገር ውስጥ ዜና

ኮሚሽኑ በሲዳማ ክልል አጀንዳ ለማሰባሰብ ያዘጋጀውን መድረክ አስጀመረ

By Melaku Gedif

August 28, 2024

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በሲዳማ ክልል አጀንዳ ለማሰባሰብ ያዘጋጀው መድረክ ዛሬ በሐዋሳ ከተማ አስጀምሯል፡፡

በመድረኩ 1 ሺህ 800 የማህበረሰብ ክፍሎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የተለያዩ ተቋማት ተወካዮች፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ተወካዮችና ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተሳትፈዋል፡፡

ለ7 ቀናት የሚካሄደው መድረኩ÷ሀገራዊ መግባባት የሚፈጥሩ አጀንዳዎች በህዝባዊ ውይይት የሚሰበስቡበት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

በፍቅርተ ከበደ