የሀገር ውስጥ ዜና

በአፍሪካውያን ባለሃብቶች የሚመሩ የማምረቻ ማዕከላት አህጉራዊ ትስስርን ያሳድጋሉ – ዋምኬሌ ሜኔ

By Melaku Gedif

August 30, 2024

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካውያን ባለሃብቶች የሚመሩ የማምረቻ ማዕከላት አህጉራዊ ትስስርን እንደሚያሳድጉ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ሴክሬታሪያት ዋና ጸሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ ገለጹ፡፡

ዋምኬሌ ሜኔ እና ልዑካቸው ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ጋር በመሆን የ”ኤኤምጂ” ሆልዲንግስ የማምረቻ ኮምፕሌክስን ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸውም÷ የኮምፕሌክሱን የማምረት ሒደትና በቅርቡ ወደ ማምረት የሚገቡ የአዳዲስ ፋብሪካዎችን ግንባታ ተመልክተዋል፡፡

ግንባታዎቹ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ የተጀመረው ሥራ ወደ አንድ ከፍታ መድረሱን የሚያሳይ እንደሆነ መገንዘባቸውን ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

ዋምኬሌ ሜኔ በበኩላቸው÷ መሰል በአፍሪውያን ባለሃብቶች የሚመሩ የማምረቻ ማዕከላት የአህጉሪቱን የእርስ በርስ የንግድ ትስስር ማሳለጥ እንደሚያስችሉ አመልክተዋል፡፡