የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ በ24 ሰዓታት 141 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ3 ሰዎች ህይወት አልፏል

By Tibebu Kebede

June 25, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 4 ሺህ 675 የላብራቶሪ ምርመራ 141 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 5 ሺህ 175 መድረሱንም የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ዛሬ ባወጡት ሪፖርት አመላክተዋል።