አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ክልሎች ለሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች የጋራ መኖሪያ ቤቶችን እየሰጠ ነው በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ ፍፁም ከእውነት የራቀ መሆኑን ገለፀ።
የከተማ አስተዳደሩ እያስገነባቸው የሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በህጋዊ መንገድ ተመዝግበው ለሚገኙ ነዋሪዎች እንጂ ለተለያዩ ክልል ሰራተኞችም ይሁን ግለሰቦች የሚሰጥበት አሰራር የለውም ብሏል የከንቲባ ጽህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ።