የሀገር ውስጥ ዜና

የእርቀ ሰላም ኮሚሽን አባላት ከአማራ ክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር እየተወያዩ ነው

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የእርቀ ሰላም ኮሚሽን አባላት ከአማራ ክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በሰላም እና ደህንነት ዙሪያ ውይይት እያደረጉ ነው።

በውይይት መድረኩ ላይ የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ላቀ አያሌው፣ የእርቀ ሰላም ኮሚሽን ሰብሳቢ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል፣ ምክትል ሰብሳቢ ወይዘሮ የትነበርሽ ንጉሴ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።