አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የእርቀ ሰላም ኮሚሽን አባላት ከአማራ ክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በሰላም እና ደህንነት ዙሪያ ውይይት እያደረጉ ነው።
በውይይት መድረኩ ላይ የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ላቀ አያሌው፣ የእርቀ ሰላም ኮሚሽን ሰብሳቢ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል፣ ምክትል ሰብሳቢ ወይዘሮ የትነበርሽ ንጉሴ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።