አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ሂደት የተመለከተ እና “ግድቡ የኔ ነው’’ በሚል መሪ ቃል ነገ የበይነ መረብ ውይይት እንደሚካሄድ በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ።
ኤምባሲው ዛሬ እንዳስታወቀው በውይይቱ በደቡብ አፍሪካና ኤምባሲው በተወከለባቸው ሰባት ሃገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም በመላው ዓለም ኢትዮጵያን የሚወክሉ ሚሲዮኖች፣ ስመጥር ምሁራንና ባለሀብቶች ተሳታፊ ይሆናሉ።