የሀገር ውስጥ ዜና

ተጨማሪ 250 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ8ሰው ህይወት አልፏል

By Feven Bishaw

June 26, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰአታት ለ5 ሺህ 414 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 250 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ ፡፡

ሚኒስትሯ በፌስ ቡክ ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ ቫይረሱ የተገኘባቸው 158 ወንድ 92 ሴቶች መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡