የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ አቃቤ ህግ በህጻናትና ሴቶች ላይ የሚፈጸም ጥቃት በቃ ሊባል ይገባል ሲል ጥሪውን አቀረበ

By Feven Bishaw

June 26, 2020

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 19 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በህጻናትና ሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን በቃ ሊባል ይገባል ሲል የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ ጥሪውን አቀረበ።

ጠቅላይ አቃቤ ህጉ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ እንዳመለከተው በዓለማችን ብሎም በአገራችን የኮሮና ቫይረስ ተግዳሮት እየተፈታተነን ባለበት ወቅት በህጻናትና በሴቶች ላይ የሚደርሰው ጥቃት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።