አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በአንጎለላና ጣራ ወረዳ በአጂማ ወንዝ ላይ በ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር የሚገነባው አጂማ- ጫጫ የመስኖ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት የኮንትራት ውል ስምምነት ተፈረመ።
ስምምነቱንም የመስኖ ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር ሚካኤል መሃሪ እና የአማራ ውሃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ዘመነ ፀሀይ በውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ በተካሄደ ስነ ስርዓት ተፈራርመዋል።