አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)በጋምቤላ ክልል የመካከለኛና የረጅም ጊዜ የልማት እቅድ አዘገጃጀትና አቀራረብ መመሪያ ላይ ከክልል እስከ ወረዳ ካሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡
በውይይቱ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ቴኩዌይ ጆክ የልማት እቅድ የአንድን ሃገር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት በተቀላጠፈና በተቀናጀ መልኩ ለመምራትና ለማስተዳደር የሚያስችል የተግባር መሳሪያ መሆኑን ገልፀዋል፡፡