የሀገር ውስጥ ዜና

በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በኖርዌይ ፓርላማ ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ

By Tibebu Kebede

July 16, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በኖርዌይ ፓርላማ ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል።

የሰልፉ ዋና ምክንያት እና ዓላማ በአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ላይ የተፈፀመውን ግድያ ተከትሎ በሽብርተኛ ተግባር ላይ በተሰማሩ አካላት ንፁሃን ኢትዮጵያውያን ሕይወት መቀጠፉ፣ ንብረት መውደሙና መፈናቀላቸውን በመቃወም ነው።