አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 6፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቶን የአፈር ማዳበሪያ ለማጓጓዝ ከሁለት ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ስምምነት ተፈራረመ።
ድርጅቱ ስምምነቱን የተፈራረመው ዲ ኤች ኤል እና ከዳይመንድ ሺፕ ቡከር ከተባሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ሲሆን፥ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቶን የአፈር ማዳበሪያ ከውጭ ሀገር ወደ አገር ውስጥ የሚጓጓዝ ይሆናል።