የሀገር ውስጥ ዜና

ድርጅቱ ከሁለት ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር የአፈር ማዳበሪያ ለማጓጓዝ የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 6፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቶን የአፈር ማዳበሪያ ለማጓጓዝ ከሁለት ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ስምምነት ተፈራረመ።

ድርጅቱ ስምምነቱን የተፈራረመው ዲ ኤች ኤል እና ከዳይመንድ ሺፕ ቡከር ከተባሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ሲሆን፥ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቶን የአፈር ማዳበሪያ ከውጭ ሀገር ወደ አገር ውስጥ የሚጓጓዝ ይሆናል።