የሀገር ውስጥ ዜና

ቼክ ሪፐብሊክ ከአብርኾት ቤተ-መጻሕፍት ጋር እንደምትሠራ አስታወቀች

By ዮሐንስ ደርበው

December 08, 2024

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ቼክ ሩፐብሊክ አዲስ አበባ ከሚገኘው አብርኾት ቤተ-መጻሕፍት ጋር ቀጣይነት ያላቸው ሥራዎችን በትብብር ለመሥራት ቁርጠኛ መሆኗን አረጋገጠች፡፡

የሀገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ማሪያን ጁሬስካ አብርኾት ቤተ-መጻሕፍትን ጎብኝተዋል፡፡

በዚሁ ወቅትም የቤተ-መጻሕፍቱ ዳይሬክተር ውብአየሁ ማሞ (ኢ/ር) ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡

ከቤተ-መጻሕፈቱ በተጨማሪም በተቋሙ ሥር ያሉ እንደ ሮቦቲክስ የመሳሰሉ ስልጠናዎች የሚሰጡባቸውን ስፍራዎች መጎብኘታቸው ተገልጿል፡፡

በዚሁ ወቅትም ማሪያን ጁሬስካ ባዩት ነገር መደነቃቸውን ገልጸው÷ ለተቋሙ መጽሐፍትን በሥጦታ አበርክተዋል፡፡

ከተቋሙ ጋርም ቀጣይነት ያላቸውን ሥራዎች ለመስራት ማረጋገጣቸውን የቤተ-መጻሕፍቱ መረጃ አመላክቷል፡፡