አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶኻን ጋር ተወያዩ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ልዑካቸው ዛሬ ከቀትር በኋላ ቱርክ-አንካራ መግባታቸው ይታወቃል፡፡
በዚሁ ወቅትም የቱርኩ ፕሬዚዳንትን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡
ሁለቱ መሪዎች ከልዑካን ቡድናቸው ጋር በመሆን በሀገራዊ የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡