የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ 24 ሰዓታት 561 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው፤ የ7 ሰዎች ሕይወት አልፏል

By Tibebu Kebede

July 21, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 6 ሺህ 544 የላብራቶሪ ምርመራ 561 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 11 ሺህ 72 መድረሱንም የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በትዊተር ገፃቸው ባወጡት መረጃ አመላክተዋል።