አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 7፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የዓለምአቀፉ ማህበረሰብ ለስደተኞች የሚሰጠው ድጋፍ እና ምላሽ የስደተኞችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አቅም ትርጉም ባለው ደረጃ ሊያጎለብት እንደሚገባው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ገልፀዋል።
“ዓለምአቀፍ የስደተኞች ፎረም” ላይ ንግግር ያደረጉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ÷ ለስደተኞች የሚደረገው ድጋፍ እና ምላሽ ትርጉም አዘል መሆን እንደሚገባው ተናግረዋል።