አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚልና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ነው።
በጉብኝታቸውም በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የመሰረተ ልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡
ሚኒስትሮቹ በክልሉ በሚኖራቸው ቆይታ በተለያዩ ዞኖች የሥራ ጉብኝት እንዲሁም ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርጉ ተጠቁሟል፡፡